
ተልዕኮ
የኢትዮጵያ ካናዳውያን አዛውንቶች ማህበር ተልዕኮ በኦታዋ አካባቢ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊ አረጋውያን፤ ሴቶችንና ወጣቶችን ለመደገፍ አስፈላጊ አገልግሎቶች በመስጠት ጠንካራና ሁሉንም ያካተተ ማህበረሰብ ማፍራት ነው፡፡ የጤናና የአካል ብቃት ወርክሾፖችንና የመረጃ ሴሚናሮችን በማዘጋጀት፤ የምግብና የትራንስፖርት አገልግሎት በማቅረብ እነዚህ የህብረተሰብ ክፍሎች ባህላዊ ቅርሶቻቸውን በመጠበቅ ጤናማና የተሻለ ማህበራዊ ግንኙነት እንዲኖራቸው ለማስቻል እንሰራ ለን። የምግብና የትራንስፖርት አገልግሎትም እንሰጣለን።ጥረታችን የማህበረሰባችን አባላት የተሻለ እርካታ የተሞላበት ህይወት ለመኖር የሚያስችላቸውን እውቀት እንዲያገኙ ማስቻል ነው፡፡
ዓላማ
ዓላማችን ማህበራችንን ለሁሉም ሰው ምቹና ተወዳጅ የአገልግሎት ማእከል ማድረግ ነው። ይህ ማህበር ለማህበረሰባችን ጥንካሬና መስተጋብር አስፈላጊ እንደሆነ እናምናለን። ለህዝባችን አስፈላጊውን እንክብካቤና እርዳታ በመስጠት፤
-
ለአረጋዊያን ደህንነቱ የተጠበቀ፣ አካታችና እንግዳ ተቀባይ አካባቢ መፍጠር፣
-
የተለያዩ የህይወት ልምድ ያላቸውን ግለሰቦች እንዲገናኙና ትስስር እንዲፈጥሩ ማስቻል፣
-
በዋጋ ተመን ሊወጣላቸው የማይችሉ እውቀቶችን ከአረጋውያን ማሰባሰብና ወደ ወጣቱ ትውልድ ማስተላልፍ፣
-
ለአረጋውያን አቅመ ደካሞች የምግብ፣ የትራንስፖርትና የሰነድ አያያዝ አገልግሎት ድጋፍ ማቅረብ፣
-
የኢትዮጵያ ካናዳውያን ወጣቶችን በማንነት ግንዛቤ፣ ባህላዊ እሴቶች እና አረጋውያንን እንዲያከብሩ በትውልዶች መካከል ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር ትምህርታዊ ፕሮግራሞችን መስጠት።